ቀደም ባለው ጊዜ በሐገራችን የሚሰራጩ የሬዲዮ እና የቴሌቪዥን ጣቢያዎቻችን ቁጥር አነስተኛ ነበር፡፡ ከ 16ዓመት በፊት FM 97.1 ሳይጀመር፤ ጣቢያዎቹ የሚያስተላልፏቸው ፕሮግራሞች በህብረተሰቡ ዘንድ ያላቸው ተቀባይነት ደግሞ ከፍተኛ ነበር፡፡ የዕጅ ሰዓትን ለመሙላት ሳይቀር ማንጸሪያ እና መከራከሪያ ነጥቡ ከራዲዩ እኩል መሆኑ ነበር፡፡ አሁን በርከት ያሉ የራዲዮ ጣቢያዎች ባለቤት ነን፡፡ /የግልም የመንግስትም/ ለኢትዩጵያዊ ታዳሚ እንዲደርሱ ታልመው የሚሰናዱ የሳተላይትና የሀገር ውስጥ ቴሌቪዥን ጣቢያዎች ቁጥርም በማሻቀብ ላይ ነው፡፡ የተአማኒነቱ ጉዳይ ግን ቀስ በቀስ እየተሸረሸረ መጥቷል፡፡ ዛሬ ዛሬ በራዲዮ ድምጽን ማሰማት የጥቂት ደቂቃዎች ሙከራ ውጤት ነው፡፡ እንደቀደመው ዘመን ከፍ ያለ ትጋት አይጠይቅም፡፡
Wednesday, October 11, 2017
Wednesday, September 6, 2017
ከ ‹ፍቅር እስከመቃብር› የተነሱ ሌሎች ኪነ-ጥበባዊ ሥራዎች
በዘመን
እና ጥበብ መጽሔታችን የሰኔ ወር እትም ‹ተወራራሽ የኪነ-ጥበብ ሥራዎች› በሚል
ርዕስ ሥር መጨዋወታችን ይታወሳል፡፡
መነሻቸውን አስቀድሞ ለታዳሚ በደረሰ የኪነ- ጥበብ ውጤት ላይ ያደረጉ ሥራዎችን በወፍ በረር ቃኝተናል፡፡ ያነሱትን የጥበብ ውጤት፤
ቀድሞ የነበረውን እንደነበረ በሌላ የጥበብ ዘውግ፤ ወይም ነባሩን ይዘው በሌላ ዓዲስ የሀሳብ መንገድ የተገለፁትን ዘርዝረናል፡፡
በእግረመንገድ ያስተዋልነውን፣ በትውስታ ማህደራችን ቀድመው የተከሰቱልንን ብቻ አነሳስተናል፡፡
ወጋችንን ስናሳርግ ‹ፍቅር እስከ
መቃብር› የተሰኘው ረዥም ልብወለድ ላይ ተመስርተው የተሠሩትን ለማነሳሳት ቃል ገብተን ነበር፡፡ ቃል አክባሪ ሆነን የዛሬውን ዋና
ርዕሰጉዳይ ከመጀመራችን በፊት ግን ሳንጠቅስ ያስተረፍናቸውን እና በሰኔው እትም ያዛነፍናቸውን እውነታዎች እናክም፡፡ በዚያውም ሐምሌ
ጠብቁን ብለን ነሐሴ ላይ ስላመጣነው ክፍል2 ጽሁፍ እና ስለተፈጠረው ስህተት እኔ እና የመጽሔቱ አዘጋጆች የየድርሻችንን አንባቢዎቻችንን
ይቅርታ እንለምናለን፡፡
Friday, June 23, 2017
ተወራራሽ የኪ-ነጥበብ ሥራዎች
ዘመናችንን በጥበብ ለመቃኘት የጀመርነውን ጉዞ ስንቀጥል የዛሬ ማረፊያችንን ተወራራሽ ጥበባት ላይ አድርገናል፡፡ በኪነ-ጥበቡ ዓለም አንድን ጥበባዊ ሥራ መነሻ በማድረግ፤ ወይም ሃሳቡን በሌላ ያልታየበት አቅጣጫ በማየት፤ ወይም ሙሉ ስራውን ወስዶ በሌላ የጥበብ ዘውግ መግለጽ እንግዳ ተግባር አይደለም፡፡
‹‹የማዕበል ዋናተኞች›› የተሰኘው የራዲዮ ድራማ ተዘፍኖለታል፡፡ ድርሰቱ የሐይሉ ጸጋዬ ነው፡፡ በወቅቱ ከፍተኛ ተደማጭነት የነበረው ሲሆን በበርካታ ታዳሚያን ልብ ውስጥ ለመግባት የቻለ ነበር፡፡ ድራማው ሲጠናቀቅ የዋናዋን ገጸባህሪ ስም ‹‹ዕፁብ ድንቅ›› ስያሜው በማድረግ ግሩም ዘፈን ተሰርቷል፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ያቀነቀነው ጎሳዬ ተስፋዬ ነው፡፡ ቆይቶ በላፎንቴኖችም ተዘፍኗል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ደግሞ በቴሌቪዥን ተከታታይ ድራማነት መጥቷል፡፡ ተቀባይነቱ በራዲዮ የነበረውን ያህል መሆኑን ግን እጠራጠራለሁ፡፡
Monday, May 15, 2017
ቴዲ አፍሮ - ከ’አቡጊዳ’ እስከ ‘ኢትዮጵያ’
በ1993 ዓ.ም ለህዝብ በቀረበው ‹‹አቡጊዳ››
በተሰኘ አልበሙ የሙዚቃ አድማጭን ቀልብ ለመግዛት በቅቷል፡፡ ‹‹ያስተሰርያል›› ፣ ‹‹ጥቁር
ሰው›› ፣ ‹‹ኢትዮጵያ›› የተሰኙ
ወጥ
የአልበም ስራዎችን እስካሁን አበርክቷል፡፡ ስለ ስራዎቹ ሲጠየቅ በዝርዝሩ ውስጥ የማያካትተው ስራም አለው፡፡ ‹‹ቴዲ›› ይሰኛል
የአልበሙ መጠሪያ - አቦጊዳ ከተሰኘው አልበሙ በፊት ከኤክስፕረስ ባንድ ጋር የተሠራ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ሚሊንየም አካባቢ የወጣው አልበሙ 2 አዳዲስ ሥራዎችን እና ከመድረክ የተቀዱ ነባር ስራዎችን አካቶ ለገበያ የቀረበ ሥራው ነው፡፡ ተሰብስበው ቢጠረዙ ከአንድ አልበም የሚተርፉ ነጠላ ዜማዎችንም በተለያየ ጊዜ አበርክቷል፡፡
Saturday, April 22, 2017
ተናጋሪ ፖስተሮች
ማስታወቂያ
ሰፊ ጽንሰ ሐሳብ ነው፡፡ በርካታ ዘርፎችም አሉት፡፡ የራሱ የክዋኔ ስርዓት እና ብልሃትም እንዲሁ…ከዚህ ሰፊ ባህር አንዲት ቀጭን
ሰበዝ መዘን ለዛሬ ጨዋታችን የሃሳብ ምህዋር መሽከርከሪያነት ልንፈቅድ ነው፡፡
በአንድ ወገን አድጓል በሌላው
አላደገም፤ በአንዱ ጎጥ ኢንዱስትሪ ነው በሌላው አይደለም፤ በአንዱ ጎራ ባህል አጥፍቷል በሌላው ይገነባል . . . እያስባለ በማከራከር ላይ ስላለው የኢትዮጵያ ፊልም ከፊልምም ስለ ፖስተሮች
/የስዕል ማስታወቂያዎች/ እናውጋ
ማሳወቅ፣ ለተጠቃሚነት መገፋፋት (ማጓጓት)፣ ዘላቂ ደንበኛ ማድረግ -ዋና ዋናዎቹ
የማስታወቂያ ዓላማዎች ናቸው፡፡ በርግጥ በማስታወቂያ ዙሪያ ስምምነት ላይ ያልተደረሰባቸው ጉዳዮች አሁንም አሉ፡፡ ማስታወቂያ ሳይንስ
ነው ወይስ ጥበብ፤ ዓላማው ማታለል፣ ማሳመን፣ ወይስ ማስገደድ . . .ሌሎችም ቁርጥ ያለ ምላሽ ያልተሰጣቸው ሃሳቦችን ከነክርክራቸው
አሁንም እንደተሸከመ ነው፡፡
Friday, January 13, 2017
መልክን የሻሩ ዘፈኖች
እያንዳንዳቸው የጥበብ ስራዎች የተሰሩበትን ዘመን አስተሳሰብ፣ ምኞት እና አኗኗር የሚያሳዩ መስታወቶች ናቸው፡፡
‹‹ፈረንጅ ሃገር ሳትሄድ ገና እዚሁ ሳለህ
የገባኸውን ቃል እንዴት ታፈርሳለህ?
የእውነት ሰው መስለኸኝ ክቡር የከበረ
ቃልኪዳኔን ይዤ ጠብቄህ ነበረ ››
የሚለው በብዙነሽ በቀለ የተዜመ ግሩም ዘፈን ብዙ ወጣቶች ለትምህርት ወደ ውጪ ሃገራት የሚሄዱበት፤ ትምህርታቸውን አጠናቀው በሚመለሱበት ጊዜ ደግሞ በአስተሳሰብ ልዩነት ወይም በሌላ የራሳቸው ምክንያት ከቀድሞ ወዳጆቻቸው የሚለያዩበት እንደነበረ መገመት ይቻላል፡፡
Monday, December 7, 2015
ያለመግባባታችን ምንጭ በጣም መግባባታችን ነው!
አየሽ እኔ እና አንቺ በጣም ተግባብተናል፡፡ ተገባብተናል፡፡ እኔ አንቺ ውስጥ. . . አንቺም እኔ ውስጥ. . .
አሳምረሽ ገብተሸኛል፡፡ በትክክል ገብቼሻለሁ፡፡ ዘላቂ መግባባታችን የወለደው አለመግባባት እዚህ ጋር ይፀነሳል፡፡
ሀሳቤን ብቻ ሳይሆን የሀሳብ መንገዴን አግኝሽዋል፡፡ የውሸቴን መነሾ እስከ መድረሻና ውጤቱ መናገር ሳልጀምር አውቀሽዋል፡፡ ፊቴ ላይ የሚሯሯጠው ደም ካዘለው ስሜት በላቀ በልቦናዬ
ያፈንኩትን ሀቅ መገንዘብ ችለሻል፡፡
ሀሳቤን ብቻ ሳይሆን የሀሳብ መንገዴን አግኝሽዋል፡፡ የውሸቴን መነሾ እስከ መድረሻና ውጤቱ መናገር ሳልጀምር አውቀሽዋል፡፡ ፊቴ ላይ የሚሯሯጠው ደም ካዘለው ስሜት በላቀ በልቦናዬ
ያፈንኩትን ሀቅ መገንዘብ ችለሻል፡፡
Wednesday, August 12, 2015
የማስታወቂያዎቻችን ነገር
‹ሱዛን ፎርማን› የተባሉ ጸሐፊ ‹‹The Media of Advertising›› በተሰኘው መጽሐፋቸው ስለ ማስታወቂያ አጀማመር
ሲገልጹ
‹‹ማስታወቂያ ስረ መሰረቱ በጥንታዊት ሮም መኳንንቶችን ለማስደሰት የሚደረጉ ድብድቦች /Gladiators/ በታላላቅ
አደባባዮች የሚካሄዱ መሆኑን የሚያስተዋውቁ፤ በመካከለኛው ዘመን የሞት ፍርድ በአደባባይ የሚፈፀም መሆኑን የሚያመላክቱ፤ በአሜሪካ
ጠረፍ በትልቁ ተፅፈው የሚንጠለጠሉ
የ ’ወንጀለኛ ይፈለጋል’ ማሳሰቢያዎች ናቸው፡፡›› ይላሉ፡፡
በግብጽ በ 3200 ዓ.ዓ አካባቢ በተሰሩ የማምለኪያ ህንፃዎች ላይ ማንኛው ንጉስ እንዳስገነባው የሚጠቁሙት ጽሁፎች ከማስታወቂያ
ይመደባሉ የሚሉ ምሁራንም አሉ፡፡
በታሪክ የመጀመሪያው ተብሎ በ (Encyclopedia Britanica,Vol 1 ,180) የተመዘገበው የጽሁፍ ማስታወቂያ
‹‹ሼም የተባለው ባሪያ ሃፑ ከተሰኘው
አሳዳሪ ተሰውሯል፡፡ ሃፑ የቴቢስ መልካም ዜጎች ሁሉ ይህን የጠፋ ባሪያ ቢመልሱለት ይወዳል፡፡ ባሪያው ባለቡናማ ዓይን ነው፡፡ ያለበትን
አካባቢ ዜና ላመጣ ግማሽ የወርቅ ሳንቲም ይሰጠዋል፡፡ ሼምን ወደአሳዳሪው ለሚመልስ ደግሞ እንደፍላጎቱ ልብስ የሚደሸመንለት ሲሆን
ሙሉ የወርቅ ሳንቲምም ይሰጠዋል፡፡››
የሚል ሲሆን ከ 3ሺህ ዓመት በፊት በፓፒረስ ላይ የተጻፈ መሆኑ ተገልጧዋል፡፡
በዘመናዊና በተደራጀ መልኩ ከቀረቡት ማስታወቂያዎች በፊት ግን ሰዎች ድምጻቸውን ከፍ በማድረግ ማስታወቂያቸውን ይናገራሉ፡፡
በሐገራችንም ይህ ተግባር የተለመደ ነበር
Tuesday, July 14, 2015
‹ስለ ኢትዮጵያ ስል ተኮላሽቻለሁ፡፡›
‹‹ፍቅር ይዞህ ያውቃል ለመሆኑ?››
‹‹አዎን››
‹‹ከማን ጋር?››
‹‹ከኢትዮጵያ››
‹‹አሃ! የፍቅረኛህ ስም ኢትዮጵያ ነበር?››
‹‹አዎን!››
‹‹ለምን ከኢትዮጵያ ጋር ተለያያችሁ?››
‹‹መንግስቱ ሃይለማርያም እና ድርጅቱ ትግላችንን እና ኢትዮጵያ ሀገራችንን ገደሏት››
‹‹ዋለልኝ! ለምን ታሾፍብኛለህ? ምንድነው የምትቀባጥረው?››
‹‹አዎን››
‹‹ከማን ጋር?››
‹‹ከኢትዮጵያ››
‹‹አሃ! የፍቅረኛህ ስም ኢትዮጵያ ነበር?››
‹‹አዎን!››
‹‹ለምን ከኢትዮጵያ ጋር ተለያያችሁ?››
‹‹መንግስቱ ሃይለማርያም እና ድርጅቱ ትግላችንን እና ኢትዮጵያ ሀገራችንን ገደሏት››
‹‹ዋለልኝ! ለምን ታሾፍብኛለህ? ምንድነው የምትቀባጥረው?››
ከጭምትነቱ ወጥቶ ጣራው እስኪሰነጠቅ ድረስ ሳቀ፡፡ ቲያትር የሚሰራ ነው የሚመስለው፡፡ ለደቂቃዎች ሳቁን
አላቆመም፡፡ ሳቁ ግን የደስታ ሳይሆን የንዴት እንደነበር ያስታውቃል፡፡ አይኖቹ እና ፊቱ ቀሉ፡፡ ደምስሮቹ በአንገቱ
እና በፊት ገጹ ላይ ተገታተሩ፡፡ የመጨረሻ ጥያቄዬ በጣም እንዳበሳጨው ተረዳሁ፤
Monday, November 17, 2014
ከብዙ ዓመታት በኋላ የሚነገር የከብዙ ዓመት በፊት ታሪክ
መግቢያ
ጥቂት የማይባሉ አያሌ ዘመናትን ወደፊት ተሻግረን ከቀናቶች መካከል ባለች የተለመደች አዘቦት ቀን ላይ ነን፡፡ ተንጠራርተን እያስተዋልናት ባለችው በዚህች ተራ ቀን ድሮ ምን ይመስል እንደነበር ልንቃኝ ነው፡፡ በአሁን የጊዜ ፈረስ ተፈናጠን ነገን በዛሬ ልናነፃፅር . . .
ትዝታ አይደለም፡፡ ትዝታ የኖሩትን በምናብ መድገም ነው፡፡ ከትውስታ ጓዳም ከህልውና መድረክም ሊሰርዙት አይቻልም፡፡ መከሰቱም ማለፉም የተረጋገጠ ነው፡፡
ትንቢት አይደለም፡፡ ትንቢት ያልኖሩትን መገመት ነው፡፡ ስምረቱንም ክሽፈቱንም ማረጋገጥ ከባድ ነው፡፡
ይህ ከሁለቱም ይለያል፡፡ ሁለቱንም መሳይ ገፅ አለው፡፡
Subscribe to:
Posts (Atom)