Saturday, April 27, 2013

ለፈገግታ


 በአንዱ የገጠር ቀበሌ ነው። ጥቂት ጎረምሶች የዓንድ ሀብታም ገበሬን በግ በመስረቅ አርደው ይበሉና የበሉበትን ሰው በቅኔ  ለመዝለፍ በማሰብ ያዘኑ መበምሰል እንዲህ ይሉታል።

እርስዎም ሳይነግሩን እኛም ሳንፈልግ
አሁን የት ይገኛል እንደርስዎ በግ

በግ መባሉን በሚገባ የተረዳውና ስራቸውንም ያወቀው፤ በጉ ተሰርቆ የተበላበት ግለሰብም እንዲህ ሲል መለሰ።

ቆየ ሰነበተ ከጠፋብኝ በጉ
እስቲ እየጋጣችሁ እናንተም ፈልጉ


No comments:

Post a Comment