"ሰስፔንድድ ኮፊ" ስለሚባል ነገር ሰምቼ እንዴት ደስ አለኝ መሰላችሁ። ነገርየው የአውሮፓውያን ባህል ነው፡፡ ወደአንድ ካፌ ቡና ለመጠጣት የገባ ገንዘብ ያለው ዓንድ ሰው ቡናውን አጣጥሞ የተጠቀመበትን ሂሳብ ሲከፍል ትርፍ ክፍያ ይፈፅማል። ማለትም አንድ ቡና ይጠጣና የሁለት ቡና የከፍላል የህንን የሚያደርገው ማንም ገንዘብ የሌለው ነገር ግን ቡና መጠጣት የፈለገ ሰው እንዲጠጣበት ነው። ሲከፍል የሚሰጠው ማረጋገጫ የለም። እርሱም አይጠይቅም። ሁሉም ነገር በእምነት ይከናወናል። ይህንን ሰስፔንድድ ኮፊ የተባለ አገልግሎት ለመጠቀም የፈለገ ሰውም "ዛሬ ሰስፔንድድ ኮፊየከፈለ አለ?" ብሎ በመጠየቅ መኖሩ ከተነገረው ከማያውቀው ሰው የተጋበዘውን ቡና ጠጥቆ አመስግኖ ይወጣል። አሪፍ አይደለች እነ ክሬዚዴይን እና አፕሪል ዘፉልን ከመኮረጅ እንደዚህ አይነቱን መኮረጅ በምድርም በሰማይም አይበጀንም ትላላችሁ? እስኪ እንወያይበት
No comments:
Post a Comment