"ሰስፔንድድ ኮፊ" ስለሚባል ነገር ሰምቼ እንዴት ደስ አለኝ መሰላችሁ። ነገርየው የአውሮፓውያን ባህል ነው፡፡ ወደአንድ ካፌ ቡና ለመጠጣት የገባ ገንዘብ ያለው ዓንድ ሰው ቡናውን አጣጥሞ የተጠቀመበትን ሂሳብ ሲከፍል ትርፍ ክፍያ ይፈፅማል። ማለትም አንድ ቡና ይጠጣና የሁለት ቡና የከፍላል የህንን የሚያደርገው ማንም ገንዘብ የሌለው ነገር ግን ቡና መጠጣት የፈለገ ሰው እንዲጠጣበት ነው። ሲከፍል የሚሰጠው ማረጋገጫ የለም። እርሱም አይጠይቅም። ሁሉም ነገር በእምነት ይከናወናል። ይህንን ሰስፔንድድ ኮፊ የተባለ አገልግሎት ለመጠቀም የፈለገ ሰውም "ዛሬ ሰስፔንድድ ኮፊየከፈለ አለ?" ብሎ በመጠየቅ መኖሩ ከተነገረው ከማያውቀው ሰው የተጋበዘውን ቡና ጠጥቆ አመስግኖ ይወጣል። አሪፍ አይደለች እነ ክሬዚዴይን እና አፕሪል ዘፉልን ከመኮረጅ እንደዚህ አይነቱን መኮረጅ በምድርም በሰማይም አይበጀንም ትላላችሁ? እስኪ እንወያይበት
Monday, April 29, 2013
Saturday, April 27, 2013
ለፈገግታ
በአንዱ የገጠር ቀበሌ ነው። ጥቂት ጎረምሶች የዓንድ
ሀብታም ገበሬን በግ በመስረቅ አርደው ይበሉና የበሉበትን ሰው በቅኔ ለመዝለፍ በማሰብ ያዘኑ መበምሰል እንዲህ ይሉታል።
እርስዎም ሳይነግሩን እኛም ሳንፈልግ
አሁን የት ይገኛል እንደርስዎ በግ
በግ መባሉን በሚገባ የተረዳውና ስራቸውንም ያወቀው፤
በጉ ተሰርቆ የተበላበት ግለሰብም እንዲህ ሲል መለሰ።
ቆየ ሰነበተ ከጠፋብኝ በጉ
እስቲ እየጋጣችሁ እናንተም ፈልጉ
ምቀኛ ፊደል
ግጥሞችን ስትሰሙ (ስታነቡ) ወይኔ ይቺ ቃል (ይቺ ፊደል) ባትኖር ብላችሁ ታቃላችሁ? እስኪ በሱ ዙሪያ የምታጠነጥን ቀልድ ላካፍላችሁ "ምቀኛ ፊደል ነው ርዕስዋ" የፑሽኪኑ የስነ-ጽሁፍ ምሽት ገናና በነበረበት ዘመን ነበር የሰማሁዋት፡፡ ማን እንዳላት አላስታውስም፡፡
ገጣሚው ግጥም ይጽፍና ቤት አልመታ ይለዋል እናም ችሎታውን ሳይሆን ፊደላትን ይረግማል ምቀኛ እያለ
እነሆ አንዱ ግጥም
ገጣሚው ግጥም ይጽፍና ቤት አልመታ ይለዋል እናም ችሎታውን ሳይሆን ፊደላትን ይረግማል ምቀኛ እያለ
እነሆ አንዱ ግጥም
Subscribe to:
Posts (Atom)