Monday, December 11, 2017

ያልተገባ አድናቆት የወለዳቸው የጥበብ ሥራዎች

ለሰሩ ሰዎች፤ ልከኛ በሆነ መንገድ ተጉዘው የራሳቸውን በጎ አሻራ ላኖሩ ጥበበኞች፤ ምስጋናን መቸር ተገቢ ነው፡፡ ለላቀው ጥበባቸው አድናቆት እና ሽልማት ማበርከት እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡ የዚህ ክዋኔ ግብረመልስ ከዋነኞቹ የአሁን ጥበበኞች በላይ ለከርሞ ተተኪዎች የጎላ ጠቀሜታ አለው፡፡ በጠንካራ ሥራዎቹ ሰበብ እውቅና የተሰጠው፤ በላቀ አበርክቶው ምክንያትነት ምስጉን ለመባል የበቃ፤ . . . የጥበብ ዋርካ ሲበረክት አርዓያ የሚያደርጉት የነገ ፍሬዎች ቁጥር እንዲያሻቅብ ያግዛል፡፡ ሁኔታው ለጠጥ ተደርጎ ሲታሰብ እንደ ሐገር እየተተካካን ሩቅ እንድንጓዝ የሚያስችለንን ነዳጅ የሚሞላልን ግብአት ነው፡፡