Monday, May 15, 2017

ቴዲ አፍሮ - ከ’አቡጊዳ’ እስከ ‘ኢትዮጵያ’


1993 . ለህዝብ በቀረበው ‹‹አቡጊዳ›› በተሰኘ አልበሙ የሙዚቃ አድማጭን ቀልብ ለመግዛት በቅቷል፡፡ ‹‹ያስተሰርያል›› ‹‹ጥቁር ሰው›› ‹‹ኢትዮጵያ››  የተሰኙ ወጥ የአልበም ስራዎችን እስካሁን አበርክቷል፡፡ ስለ ስራዎቹ ሲጠየቅ በዝርዝሩ ውስጥ የማያካትተው ስራም አለው፡፡ ‹‹ቴዲ›› ይሰኛል የአልበሙ መጠሪያ - አቦጊዳ ከተሰኘው አልበሙ በፊት ከኤክስፕረስ ባንድ ጋር የተሠራ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ሚሊንየም አካባቢ የወጣው አልበሙ 2 አዳዲስ ሥራዎችን እና ከመድረክ የተቀዱ ነባር ስራዎችን አካቶ ለገበያ የቀረበ ሥራው ነው፡፡ ተሰብስበው ቢጠረዙ ከአንድ አልበም የሚተርፉ ነጠላ ዜማዎችንም በተለያየ ጊዜ አበርክቷል፡፡