Friday, January 13, 2017

መልክን የሻሩ ዘፈኖች

እያንዳንዳቸው የጥበብ ስራዎች የተሰሩበትን ዘመን አስተሳሰብ፣ ምኞት እና አኗኗር የሚያሳዩ መስታወቶች ናቸው፡፡

‹‹ፈረንጅ ሃገር ሳትሄድ ገና እዚሁ ሳለህ

የገባኸውን ቃል እንዴት ታፈርሳለህ?

የእውነት ሰው መስለኸኝ ክቡር የከበረ

ቃልኪዳኔን ይዤ ጠብቄህ ነበረ ››

የሚለው በብዙነሽ በቀለ የተዜመ ግሩም ዘፈን ብዙ ወጣቶች ለትምህርት ወደ ውጪ ሃገራት የሚሄዱበት፤ ትምህርታቸውን አጠናቀው በሚመለሱበት ጊዜ ደግሞ በአስተሳሰብ ልዩነት ወይም በሌላ የራሳቸው ምክንያት ከቀድሞ ወዳጆቻቸው የሚለያዩበት እንደነበረ መገመት ይቻላል፡፡