Tuesday, July 14, 2015

‹ስለ ኢትዮጵያ ስል ተኮላሽቻለሁ፡፡›

‹‹ፍቅር ይዞህ ያውቃል ለመሆኑ?››
‹‹አዎን››
‹‹ከማን ጋር?››
‹‹ከኢትዮጵያ››
‹‹አሃ! የፍቅረኛህ ስም ኢትዮጵያ ነበር?››
‹‹አዎን!››
‹‹ለምን ከኢትዮጵያ ጋር ተለያያችሁ?››
‹‹መንግስቱ ሃይለማርያም እና ድርጅቱ ትግላችንን እና ኢትዮጵያ ሀገራችንን ገደሏት››
‹‹ዋለልኝ! ለምን ታሾፍብኛለህ? ምንድነው የምትቀባጥረው?››


ከጭምትነቱ ወጥቶ ጣራው እስኪሰነጠቅ ድረስ ሳቀ፡፡ ቲያትር የሚሰራ ነው የሚመስለው፡፡ ለደቂቃዎች ሳቁን አላቆመም፡፡ ሳቁ ግን የደስታ ሳይሆን የንዴት እንደነበር ያስታውቃል፡፡ አይኖቹ እና ፊቱ ቀሉ፡፡ ደምስሮቹ በአንገቱ እና በፊት ገጹ ላይ ተገታተሩ፡፡ የመጨረሻ ጥያቄዬ በጣም እንዳበሳጨው ተረዳሁ፤