አንድ
ወዳጅ ነበረኝ “ እግዚአብሄር የሚወድህ ከሆነ ገንዘብ አይሰጥህም !” የሚለኝ። ዝና አይሰጥህም፤ ስልጣን አይሰጥህም፤ ይላል። እነዚህ ሁሉ ሲመነዘሩ ሰውን አይተኩማ፣ ሰውን ከማግኘት ጋር አይተካከሉማ፣ እግዚአብሄር የሚወድህ ከሆነ ሰው ይሰጥሀል። በጎደለ የምትሞላው፣ ክፍተትህን የምትዘጋበት፣ ዕውቀትም ገንዘብም የሆነ . . . ስልጣንም ዝናም የሚሰጥህ ሰው።
ዲዮጋንን በጠራራ ፀሀይ ፋኖስ አስይዞ ያስፈለገው ሰው። ባለቅኔው “የሰው ያለህ የሰው” ብሎ እንዲቀኝ ያስገደደው ሰው። ለዘመናት ድሮ ቀረ . . .ድሮ አልቀረ እያስባለ እልባት አልባ ክርክር ያከራከረው ሰው። ኢየሱስ፣ ቡድሀ፣ መሀመድ ያላቸውን ነገር ሁሉ የከፈሉለት ሰው።
እኔም እናንተ አላችሁኝ እላለሁ። የድክመቴ አበርቺ፣ የጥንካሬዬ ጠቋሚ፣ የሽንፈቴ አፅናኝ፣ የሀሴቴ አድማቂ፣ የጉዳቴ ተሟጋች . . . የሁለ ነገሬ ሁሉም ነገሮች አላችሁኝ እላለሁ። ኑሩልኝ። እደግመዋለሁ ኑሩልኝ።
ዲዮጋንን በጠራራ ፀሀይ ፋኖስ አስይዞ ያስፈለገው ሰው። ባለቅኔው “የሰው ያለህ የሰው” ብሎ እንዲቀኝ ያስገደደው ሰው። ለዘመናት ድሮ ቀረ . . .ድሮ አልቀረ እያስባለ እልባት አልባ ክርክር ያከራከረው ሰው። ኢየሱስ፣ ቡድሀ፣ መሀመድ ያላቸውን ነገር ሁሉ የከፈሉለት ሰው።
እኔም እናንተ አላችሁኝ እላለሁ። የድክመቴ አበርቺ፣ የጥንካሬዬ ጠቋሚ፣ የሽንፈቴ አፅናኝ፣ የሀሴቴ አድማቂ፣ የጉዳቴ ተሟጋች . . . የሁለ ነገሬ ሁሉም ነገሮች አላችሁኝ እላለሁ። ኑሩልኝ። እደግመዋለሁ ኑሩልኝ።